(ግንቦት 22/2017 ዓ.ም) የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በቀጣይ ለሚወስዱት ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በቂ ዝግጅት ለማድረግ እገዛ የሚያደርግ ሞዴል ፈተና ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው እለት ተጠናቋል።
ሞዴል ፈተናው ተማሪዎቹ ለመደበኛው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉ ስታንዳርዱን የጠበቀ ፈተና ስለሆነየትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር አቶ ዘነበ ፈተናው በአግባቡ እንዲሰጥ ድጋፍና ክትትል የሚያደርጉ ባለሙያዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።